የአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጅ ዩኒቨርሲቲ 2014 ዓ.ም የፊዚክስ እና የሂሳብ ትምህርት ተመራቂው ራጂ አሸናፊ 60 የትምህርት አይነቶችን A+ በማምጣት ታሪክ ሰርቷል።

አዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጅ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ መስኮች ሲያሰለጥናቸው የቆዩ 1 ሺህ 253 ተማሪዎችን አስመርቋል።

የ25 አመቱ ወጣት ራጂ በአዳማ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የፊዚክስ እና የሂሳብ ትምህርት ተመራቂ ሲሆን በ60 የትምህርት አይነቶች A+ በማምጣት አስገራሚ ውጤት አስመዝግቧል።

ራጂ ተወልዶ ያደገው ቄለም ወለጋ ጊዳሚ ከተማ ሲሆን የ10ኛ ክፍል ውጤቱ በሁሉም የትምህርት ዓይነቶች A እንደነበር እና የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ውጤቱም 647 እንደነበር ተገልጿል።

በዓለም ላይ ካሉት የሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲዎች ግንባር ቀደም የሆነው ኤም አይ ቲ ራጂ እስከ ፒ ኤች ዲ ድረስ በዩኒቨርሲቲው ተቀላቅሎ እንዲማር ነጻ የትምህርት እድል ለመስጠት ቃል እንደገባላቸውም የአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶክተር ለሚ ጉታ ተናግረዋል ሲል ኤፍቢሲ ዘግቧል።

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

%d bloggers like this: